Wednesday, March 7, 2018

ሳምንቱ በታሪክ


የጥናት ስምምነት




ኢትዮጵያና ጃፓን ለመጀመሪያ ጊዜ የአጋርነት እና የንግድ ውልን በመፈራረም ግንኙነታቸውን የጀመሩት 1922 . (1930 ..) ነበር:: ሁለቱ አገራት ይህን ስምምነት በተፈራረሙ በዓመቱ በወቅቱ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የነበሩት ህሩይ ወልደ ስላሴ ጃፓንን ለመጐብኘት ሄዱ:: በዚህ ጉብኝት ወቅትም የአገሪቱን ግንኙነት ወደ ኢኮኖሚያዊ እና ወታደራዊ አጋርነት የሚያሸጋግር ሌላ ስምምነት ተፈራረሙ::

የሁለቱ አገራት ግንኙነት ጣሊያን ኢትዮጵያን በመውረሯ እና ጃፓን ደግሞ ከኢትዮጵያ ጐን ባለመቆሟ ብሎም ሁለተኛው የአለም ጦርነት ሲጀምር ጃፓን ከነጣሊያን ጋር በማበሯ ተቋረጠ:: 20 ዓመታት በኋላም ማለትም 1947 . አካባቢ የሁለቱ አገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በአዲስ ተጀመረ:: ግንኙነቱ እየተጠናከረ ሄዶም ከሶስት አመታት በኋላ አምባሳደሮችን በየአገሪቱ ሾሙ::

ይህ የሁለቱ አገራት የአጋርነት እና ትብብር ስምምነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጠናከረ መሄዱን ተከትሎ በኢትዮጵያ የተለያዩ ግዛቶች የመልክአምድር ጥናት ለማድረግ የሚያስችሉ ስምምነቶች ላይ ሊደረሱ ችለዋል:: ታዲያ በተመሳሳይ በወለጋ ጠቅላይ ግዛት የመልክአምድር ጥናት እንዲደረግ በኢትዮጵያ እና በጃፓን መንግሥታት መካከል ስምምነት የተፈረመው በዚህ በያዝነው ሳምንት የካቲት 29 ቀን 1965 . ነበር::

የጋዜጠኞች መባረር

በኢትዮጵያ የነበረው ዘውዳዊ አገዛዝ ህብረተሠቡን እኩል የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚ ካለማድረጉም ባሻገር በአገሪቱ ጭቆና እንዲንሰራፋ በማድረጉ የብሶት ድምፆች መሰማት ጀመሩ:: እነዚህ የብሶት ድምፆች በገበሬዎች፣ በወታደሮች፣ በምሁራንና በተማሪዎች በኩል በየጊዜው የተለያዩ ጥያቄዎችን እያነሱ ማሰማት ጀመሩ:: በተለይ 1960ዎቹ መጀመሪያ ጀምሮ የብሶት ድምፆች እየተጠናከሩ እና እየተባባሱ መጡ::

የብሶት ጥያቄዎቹ እየተባባሱ ቢሄዱም ከዘውዳዊው አገዛዝ አራማጆች በኩል ግን ይህን ብሶት የሚያረግብ ምላሽ ሊገኝ አልቻለም:: በተለያዩ አካባቢዎችም የተማሪዎች እንቅስቃሴዎች ተጠናክረው ቀጠሉ::

ታዲያ ለእነዚህ የተማሪዎች እንቅስቃሴዎች የገንዘብ እርዳታ አድርገዋል በሚል በኢትዮጵያ ውስጥ ይሰሩ የነበሩ ሶስት የሩሲያ ጋዜጠኞች እና ሶስት የቼኮዝሎቫኪያ ዲፕሎማቶች ከአገሪቱ እንዲባረሩ የተደረገው በዚህ በያዝነው ሳምንት መጋቢት ሁለት ቀን 1961 . ነበር::

ምንጭ በኩር የካቲት 28 ቀን 2008 .


No comments:

Post a Comment